Saturday, 18 August 2018 09:26

የጃሉድ አዲስ አልበም ረቡዕ ይለቀቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 የድምፃዊ ጃሉድ አወል “ንጉሥ” የተሰኘ አዲስ አልበም የፊታችን ረቡዕ ለአድማጭ እንደሚቀርብ የአልበሙ ፕሮዲዩሰር አይንአዲስ ተስፋዬ (ዲጄ ፒቹ) አስታወቀ፡፡ ተሰርቶ ለመጠናቀቅ ሁለት ዓመታትን የፈጀውና 1.6 ሚ. ብር እንደወጣበት የተነገረው አልበሙ፤ 17 ዘፈኖችን እንዳካተተና ቅንብሩም በካሙዙ ካሳ (ሻኩራ ስቱዲዮ) እንደተሰራ ተገልጿል፡፡
በድምፅ ቀረፃና ሚክሲንግ ይትባረክ ክፍሉና በማስተሪንጉ አበጋዝ ክብረወርቅ ሺዎታ ተሳትፈውበታል ተብሏል፡፡ የድምፃዊው ሁለተኛ የሆነው አልበሙ በአገር ፍቅርና በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረጉ ዘፈኖችን እንደተካተቱበት ፕሮዲዩሰሩ አይንአዲ ተስፋዬ (ዲጄ ፒቹ) ተናግሯል፡፡

Read 1270 times