Monday, 20 August 2018 00:00

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ታዳጊዎች ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 “የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ታዳጊዎች ፌስቲቫል” የተሰኘ በታዳጊዎች የበጎ አድራጎት የባህል፣ የኪነ ጥበብ፣ የተሰጥኦ ማሳያ፣ የግብይት፣ የቁጠባ፣ የጨዋታና የውድድር ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው፡፡
በዚህ ፌስቲቫል ላይ ታዳጊ ወጣቶች ታላቅ ራዕይ ያላቸው፣ በራሳቸው የሚተማመኑ፣ በአገራቸው ምርት የሚኮሩ፣ በበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ የሚሳተፉ እንዲሆኑ የሚያበረታቱ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተገልጿል፡፡
የፌስቲቫሉ አዘጋጆች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ፌስቲቫሉ ታዳጊዎች ቁምነገርን በቀልድና በጨዋታ በማዋዛት የሚገነዘቡበት፣ የቁጠባ ባህላቸውን የሚያዳብሩበት የግል ተሰጥኦዋቸውን በማሳየት የሚወዳደሩበትና የሚሸለሙበትን ዝግጅቶች አካትቷል፡፡
ልደታ አካባቢ በሚገኘው የልደታ መርካቶ ገበያ አዳራሽ ውስጥ ከነሐሴ 20 እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2010 ዓ.ም በሚካሄደው በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የተለያዩ የበዓል ዝግጅቶች፣ የሰርከስ ትርዒቶችና ሌሎችም በርካታ የመዝናኛ ፕሮግራሞች እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ፌስቲቫሉን ሻክርክስ ንግድና ኤቨንትስ ማኔጅመንት ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በትብብር ያቀርበዋል ተብሏል፡፡  

Read 3774 times