Saturday, 25 August 2018 12:59

ሊቢያ 700 ሺህ ስደተኞች ከግዛቷ እንዲወጡላት ጠየቀች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በተባበሩት መንግስታት የሚደገፈው የሊቢያ መንግስት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ አገሪቱ የገቡ ከ700 ሺህ በላይ የተለያዩ አገራት ስደተኞችን በቀጣይነት በግዛቱ ውስጥ የማስፈር ግዴታ እንደሌለበት በመግለጽ፣ ስደተኞቹ ወደየ አገራቸው መመለስ አለባቸው ሲል አቋሙን ማስታወቁን ዥንዋ ዘግቧል፡፡
ሊቢያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የተለያዩ አገራት ስደተኞች በግዛቷ እንድታሰፍር በተመድ የቀረበው ሃሳብ ኢ-ፍትሃዊ ነው፤ ስደተኞቹ ወደየመጡበት መመለስ አለባቸው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሞሃመድ ሳያላ ባለፈው ረቡዕ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡
የስደተኞች መተላለፊያ በመሆን ከፍተኛ መስዋዕትነት ስትከፍል የኖረቺው ሊቢያ፣ ስደተኞችን በግዛቷ የምታሰፍርበት ሁኔታ ላይ አይደለችም ያሉት ሚኒስትሩ፤አለማቀፉ ማህበረሰብ የአገራት መንግስታት በሊቢያ የሚገኙ ስደተኛ ዜጎቻቸውን መልሰው እንዲወስዱ ጫና ማድረግ ይገባቸዋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በሊቢያ የሚገኙ የስደተኞች ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ድንበር አቋርጠው በሜዲትራኒያን ባህር በኩል በጀልባ ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት ሲሞክሩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋሉና ከአሰቃቂ የባህር ላይ አደጋዎች በተረፉ በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ አገራት ህገወጥ ስደተኞች ተጨናንቀው እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፤ ስደተኞቹ በአፋጣኝ ወደ አገሮቻቸው ካልተመለሱ ከፍተኛ ቀውስ ሊፈጠር እንደሚችል መሰጋቱንም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2149 times