Saturday, 15 September 2018 00:00

“የሞሮኮ አገር እውነት” ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


    ሚዩዚክ ሜይ ዴይ ከኢትዮጵያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ በአርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው “የሞሮኮ አገር እውነት” መፅሐፍ ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ገጣሚና ጋዜጠኛ ዮሐንስ ገ/መድህን ሲሆኑ መድረኩም በሰለሞን ተሰማ ጂ እንደሚመራ ታውቋል፡፡
ደራሲው አርክቴክት ሽፈራውም በፕሮግራሙ ላይ የሚታደም ሲሆን፤ በውይይቱ ላይ ፍላጐት ያለው እንዲሳተፍ አዘጋጁ ጋብዟል፡፡


Read 1035 times