Saturday, 22 September 2018 15:11

በ‹‹ኢነር ዚል ሬጌ ሮቢክስ›› ልዩ ስልጠና ተዘጋጅቷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ጃማይካዊቷ ዜላ ግሪፍትስ ጌይል  ከክሁል ሆሊስቲክ ዴቨሎፕመንት ማዕከል ጋር በመተባበር ‹‹ኢነር ዚል ሬጌ ሮቢክስ›› የሚባለውን ልዩ የዳንስና ኤሮቢክስ እንቅስቃሴ ልታሰለጥን ነው፡፡ ልዩ የዳንስና ኤሮቢክስ እንቅስቃሴ  ስልጠናው ደምበል አካባቢ በሚገኘው ሬቲና ህንፃ 9ኛ ፎቅ ላይ ነገ በ10 ሰዓት የሚጀመር ሲሆን በየሳምንቱ እሁድ እንደሚቀጥል የዳንስ አሰልጣኟ ዜላ ግሪፍትስ ጌይል ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡
 ነገ በክሁል ሆሊስቲክ ዴቨሎፕመንት ማዕከል ለስልጠናው በተዘጋጀው የመክፈቻ ስነስርዓት የአፍሮ ቢትና የአፍሮ ሬጌ ዳንስ አሰልጣኞች እንዲሁም የዮጋ ኢንስትራክተር በተጋባዥነት ይሳተፉበታል፡፡ የ‹‹ኢነር ዚል ሬጌ ሮቢክስ›› ስልጠናው ለሁሉም የእድሜ ደረጃ እና ፆታ እንደሚሆን ሲታወቅ ክፍያው በግለሰብ ለአንድ ቀን 200 ብር እንዲሁም ለአንድ ወር 600 ብር እንደሆነ ተገልጿል፡፡  ዜላ ግሪፍትስ ጌይል  በእንግሊዝ ሳውዝሃምፐተን ከሚገኘው ዩኒቨርስቲ ኦፍ ዊንቸስተር በዳንስ ሙያ ማሰትሬት ዲግሪዋን ያገኘች ሲሆን ‹‹ኢነር ዚል ሬጌ ሮቢክስ›› የምትለውን ልዩ አይነት የዳንስ እንቅስቃሴ በመፍጠር ስትንቀሳቀስ ከ15 ዓመታት በላይ ሆኗታል፡፡ ‹‹ኢነር ዚል ሬጌ ሮቢክስ›› በዳንስ ችሎታ እያንዳንዱ ሰው ያለውን ውስጣዊ  ኃይልና ፈጠራ ከኤሮቢክስ በማጣመር እየተዝናና የሚንቀሳቀስበት ነው፡፡ በኢትዮጵያ መኖር ከጀመረች ከ8 ዓመታት በላይ የሆናት ዜላ ግሪፍትስ ጌይል፤ በዳንስ አሰልጣኝነት እና አስተማሪነት በሳንፎርድ ኢንተርናሽናል ስኩል፤ በላዮንሃርት፡ በማያ እና በአንድነት አካዳሚዎች ስታገለግል ቆይታለች፡፡

Read 3752 times