Saturday, 29 September 2018 14:44

በያሬድ ጥበቡ “ወጥቼ አልወጣሁም” ላይ ውይይት ይደረጋል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

 በዘመራ መልቲ ሚዲያና በሰለሞኒክ ኢንተርቴይንመንት በየዓመቱ የሚዘጋጀው ሁለተኛው ዙር ‹‹ጣና አዋርድ የዛሬ ሳምንት ምሸት ላይ ባህርዳር ከተማ በሚገኘው ብሉ ናይል ሪዞርት ሆቴል እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡
ሽልማቱ በዋናነት ማኅበራዊ ሚዲያን በኃላፊነት በመጠቀም ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ተወዳድረው የሚያሸንፉበት ሲሆን በፈጣን ወቅታዊና ሚዛናዊ መረጃ፣ በባህልና ቱሪዝም፣ በስፖርት መረጃ፣ በስነ-ጥበባዊ ምስሎችና ትርክቶች፣ በፎቶግራፍ፣ በሥነ-ጽሁፍ፣ በታሪክ፣ በንግድና ቢዝነስ፣ በትምህርትና ማኅበረሰብ ግልጋሎት፣ በጥናትና ምርምር፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ  እንዲሁም በበጐ አድራጐና አካባቢ ልማት ዘርፎች ግለሰቦችና ድርጅቶች እንደሚሸለሙ አዘጋጆቹ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የሽልማት ድርጅቱ በመጀመሪያው ዙር በ10 ዘርፎች አሸናፊዎችን መሸለሙ አይዘነጋም፡፡

Read 3091 times