እናት የማስታወቂያ ድርጅት ከጎተ ኢንስቲትዩትና ከብሔራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር፣ “የኢትዮ አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት” በተሰኘው የአንጋፋው ደራሲ ንጉሴ አየለ ተካ መፅሐፍ ላይ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የታሪክ ምሁሩ ረ/ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ሲሆኑ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ አዘጋጁ ጋብዟል፡፡
Saturday, 06 October 2018 11:06
“የኢትዮ አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት” ላይ ዛሬ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና