በ”ጉዞ ሚዲያና ማስታወቂያ” በየወሩ የሚዘጋጀው “ብራና ጃዝ” የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ምሽት፣ ኢትዮጵያዊ አንድነትን የሚያፀኑ ልዩ ልዩ ጥበባዊ ክዋኔዎች እንደሚቀርቡ የተገለጸ ሲሆን አንጋፋው ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ አስቴር በዳኔ፣ ሰለሞን ሳህለና ትዕግሥት ማሞ በመሶብ ባህላዊ ባንድ ታጅበው ግጥሞቻቸውን ያነባሉ ተብሏል፡፡
በተጨማሪም ጋዜጠኛና አክቲቪስት እስክንድር ነጋና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ዲስኩር የሚያቀርቡ ሲሆን በአንጋፋው አርቲስት ተስፋዬ ገ/ሃና አጭር ተውኔት፣ በወጣቷ ፀሐፊ ፅጌረዳ ጎንፋ ደግሞ ወግ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና