Monday, 15 October 2018 00:00

የአለማችን ቢሊየነሮች በአንድ ቀን 99 ቢሊዮን ዶላር ከስረዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ረቡዕ በአለማቀፍ ደረጃ የአክሲዮን ገበያ ዋጋ ቅናሽ መከሰቱን ተከትሎ፣ የአለማችን 500 እጅግ ባለጸጋ ቢሊየነሮች በዕለቱ በድምሩ 99 ቢሊዮን ዶላር ያህል ኪሳራ እንዳጋጠማቸው ተነግሯል፡፡
ከአለማችን ባለጸጎች በዕለቱ ከፍተኛውን ኪሳራ ያስተናገዱት የአማዞን ኩባንያ መስራች አሜሪካዊው ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ ሲሆኑ፣ ባለጸጋው ረቡዕ እለት 9.1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ኪሳራ እንደደረሰባቸው ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
በአለማቀፉ የአክሲዮን ገበያ ላይ በተከሰተው በዚህ ቀውስ ሳቢያ ከተጣራ ሃብታቸው ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የቀነሰባቸው የአለማችን ቢሊየነሮች 17 ናቸው ያለው ዘገባው፤ የአለማችን የቴክኖሎጂው ዘርፍ 67 ባለጸጎችም በድምሩ 32.1 ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸውን አመልክቷል፡፡
በአንድ ቀን (ረቡዕ) ቢሊየነሮቿ በከፍተኛ ሁኔታ የከሰሩባት አገር አሜሪካ ናት ያለው ዘገባው፣ የአገሪቱ ቢሊየነሮች በድምሩ 54.5 ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸውንም ገልጧል፡፡


Read 3818 times