Saturday, 20 October 2018 13:20

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕ/ት ከእስር ለማምለጥ ሞክረዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሃመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ)፤ የታሰሩበትን ክፍል መስኮት በመስበርና ከጥበቃ ጋር በመተናነቅ የማምለጥ ሙከራ አድርገው ነበር ሲል ፖሊስ ትናንት ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተናገረ ሲሆን ግለሰቡ ግን ድርጊቱን አለመፈጸማቸውን ለችሎቱ መግለጻቸውን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል፡፡
አብዲ ሞሃመድ ኡመር፤ በምርመራ ወቅት ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እንደነበረባቸውና የአእምሮ ጤና ችግር ካለበት አንድ ታሳሪ ጋር በአንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ ታስረው እንደነበር ለችሎቱ አቤቱታቸውን ማሰማታቸውን ተከትሎ ፖሊስ በሰጠው ምላሽ፣ ግለሰቡ የጤና ችግር እንዳለባቸው በመግለጻቸው ለቢሮ በሚያገለግል ክፍል ውስጥ ታስረው እንደነበርና የማምለጥ ሙከራ ካደረጉ በኋላ ግን፣ ወደ መደበኛ የእስረኞች ክፍል ተዛውረው ለብቻቸው እንዲታሰሩ ተደርጓል ማለቱን ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 2900 times