Saturday, 20 October 2018 13:43

የተፈጥሮ አደጋ በመላው አለም ከ1.3 ሚ. በላይ ሰዎችን ለሞት ዳርጓል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከ4.4 ቢሊዮን በላይ ሰዎች የተለያዩ ጉዳቶች ደርሶባቸዋል


    በአለማችን የተለያዩ አገራት ባለፉት 20 አመታት የተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ማስታወቁን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
በተፈጥሮ አደጋዎች ሳቢያ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለህልፈተ ህይወት ከተዳረጉት 1.3 ሚሊዮን ሰዎች መካከል 56 በመቶው በርዕደ መሬትና በሱናሚ ሳቢያ የሞቱ መሆናቸውን ያስታወቀው ሪፖርቱ፣ የተፈጥሮ አደጋዎች ለሞት ከዳረጓቸው ሰዎች በተጨማሪ በ4.4 ቢሊዮን ሰዎች ላይ የመቁሰልና ከመኖሪያ መፈናቀልን ጨምሮ የተለያዩ ጉዳቶችን ማድረሳቸውንም አመልክቷል፡፡
የተፈጥሮ አደጋዎች በአለማችን ህዝቦች ላይ የሚያስከትሉት ሁለንተናዊ ጉዳት ባለፉት 20 አመታት በ151 በመቶ ያህል መጨመሩን የገለጸው ሪፖርቱ፤ በአለማችን የተለያዩ አገራት ርዕደ መሬት፣ እሳተ ገሞራ፣ ጎርፍና ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎች ያስከተሉት ውድመት 2.9 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚገመትም አብራርቷል፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ የተፈጥሮ አደጋዎች 944 ቢሊዮን ዶላር ያህል ያወደሙባት አሜሪካ፣ ከአየር ንብረት ጋር ተያያዥ የሆነ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ኪሳራ የገጠማት የአለማችን ቀዳሚዋ አገር መሆኗን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ቻይና፣ ጃፓን፣ ህንድና ፖርተሪኮ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውንም አመልክቷል፡፡

Read 1609 times