Monday, 22 October 2018 00:00

የ29 ሚሊዮን ፌስቡክ ተጠቃሚዎች መረጃ ተሰርቋል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የኢንተርኔት ቁልፍ ሰባሪዎች የ29 ሚሊዮን ያህል የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን አካውንቶች ሰብረው በመግባት መረጃዎቻቸውን መመንተፋቸውን ዴችዌሌ ዘግቧል፡፡
መረጃ መንታፊዎቹ፣ የፌስቡክ ተጠቃሚዎቹን ስም፣ የኢሜይል አድራሻና የስልክ ቁጥሮች ጨምሮ ሌሎች ድብቅ መረጃዎች ፈልፍለው ማግኘታቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ፌስቡክ ኩባንያ ጥቃቱ ለደረሰባቸው ደንበኞቹ የማስጠንቀቂ መልዕክቶችን እንደሚልክ ማስታወቁንም አመልክቷል፡፡
በቅርቡ በተደረጉ ተመሳሳይ የመረጃ ምንተፋዎች ሰለባ ከሆኑት የፌስቡክ አካውንቶች መካከል፣ የኩባንያው መስራች የማርክ ዙክበርግ አካውንት አንዱ እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 5174 times