Saturday, 03 November 2018 16:01

አራት መንፈሳዊ መፅሐፍት ይመረቃሉ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማህበረ ቅዱሳን ያሳተማቸው አራት መንፈሳዊ መፅሐፍት፣ በማህበረ ቅዱሳን ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ 11 ሰዓት  ይመረቃሉ፡፡
መጽሐፍቱ “ባህልና ክርስትያናዊ ትውፊት በኢትዮጵያ”፣ “ገድለ ሰማዕታት”፣ “ሰማዕትነት በክርስትና” እና “የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ” የተሰኙት ሲሆኑ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና የሚዲያ አካላት በተገኙበት በደማቅ ስነ ስርዓት እንደሚመረቁ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከምረቃ ሥነስርዓቱ ጎን ለጎን በመፅሐፍቱ ላይ ዳሰሳና የኪነ ጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡

Read 5048 times