በመላው አለም በሚገኙ የተለያዩ አገራት ባለፉት አስር አመታት በድምሩ ከ1 ሺህ በላይ ጋዜጠኞች እንደተገደሉና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በየዕለቱ በአማካይ አንድ ጋዜጠኛ እንደተገደለ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው መረጃ እንዳለው፣ ጋዜጠኞቹ ዘገባዎችን በሚሰሩበትና ለህዝብ በሚያቀርቡበት ወቅት በስራ ገበታቸው ላይ እያሉ የተገደሉ ናቸው፡፡ባለፉት አስር አመታት በእነዚህ ጋዜጠኞች ላይ ግድያ ከፈጸሙት ሰዎች መካከል 90 በመቶ የሚሆኑት ግድያውን በመፈጸማቸው በህግ ተጠያቂ እንዳልተደረጉና እንዳልተቀጡ ድርጅቱ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡በአለማችን የተለያዩ አገራት ግድያን ጨምሮ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እያደገ መጥቷል ያለው ተቋሙ፣ መንግስታት በመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም የሚገፋፉ የጥላቻ ንግግሮችንና አባባሽ ድርጊቶችን እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ