Saturday, 03 November 2018 16:07

በ4 ወራት 1.1 ሚሊዮን ናይጀሪያውያን ወደ ከፋ ድህነት ገብተዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በአገሪቱ ከ88 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በከፋ ድህነት ውስጥ ይገኛሉ

    ባለፉት አራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ናይጀሪያውያን ወደ ከፋ ድህነት መግባታቸውንና በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር 88 ሚሊዮን መድረሱን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
ተቀማጭነቱን በቪየና ያደረገው ወርልድ ፖቨርቲ ክሎክ የተሰኘ ተቋም ይፋ ባደረገው አለማቀፍ ሪፖርት እንዳለው፣ ከ1.9 ዶላር በታች ዕለታዊ ገቢ ባላቸው ወይም በከፋ ድህነት ውስጥ በሚገኙ ዜጎች ብዛት ናይጀሪያ ከአለማችን አገራት በቀዳሚነት ትገኛለች፡፡
በናይጀሪያ ድህነት ስር እየሰደደ እንደሚገኝ የጠቆመው ተቋሙ፣ መንግስት ችግሮችን ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑንና አገሪቱ በ2030 ከድህነት ለመውጣት ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት እንደማትችል የሚያመላክቱ ሁኔታዎች መኖራቸውንም አስረድቷል፡፡ የቢልና ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ያወጣውን ትንበያ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በመጪዎቹ 12 አመታት ጊዜ ውስጥ ከአለማችን እጅግ ድሃ ሰዎች መካከል ከ40 በመቶ በላይ የሚሆኑት በናይጀሪያ እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡
የአለም ባንክ በበኩሉ፤ በመላው አለም በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ቁጥር ከ1.6 ቢሊዮን በላይ መድረሱን ያስታወቀ ሲሆን፣ ከ29 በመቶ በላይ የሚሆኑትም ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገራት እንደሚኖሩ አስረድቷል፡፡


Read 1581 times