Print this page
Saturday, 10 November 2018 13:16

ጀግንነት በየፈርጁ!

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በአሜሪካ ሚኔሶታ ግዛት ነው፡፡   
ለአሜሪካዊው የእሳት አደጋ ሠራተኛ ጀሬሚ ቦሮሳ ልዩ ቀን ነበረች፡፡ ከወደፊት የህይወት አጋሩ ክሪስታ ቦላንድ ጋር ትዳር የሚመሰርቱበት የጋብቻ  ዕለት፡፡ ሙሽሮቹና ጥቂት ዘመድ ወዳጆቻቸው፣ የማስታወሻ ፎቶግራፍ ለመነሳት፣ የእሳት አደጋ መከላከያ ጣቢያው ጋ ተሰባስበው ነበር፡፡ ይሄን ጊዜ ነው  ቦሮሳ  ከሥራ ባልደረቦቹ  ያልጠበቀው የስልክ ጥሪ የደረሰው፡፡ በአቅራቢያ በሚገኝ የመኖሪያ ቤት ላይ  የእሳት ቃጠሎ ደርሶ፣ የሰው ሃይል ስላነሳቸው ነበር  የደወሉለት፡፡ ጀሬሚ ቦሮሳ  እረፍት ላይ  ቢሆንም፣ ለባልደረቦቹ ድንገተኛ የእርዳታ ጥያቄ ጆሮ ዳባ ልበስ አላለም፡፡ ከመቅጽበት የሠርግ ሥነስርዓቱን አቋርጦ ሄደ እንጂ፡፡ በደቂቃዎች ውስጥም ዩኒፎርሙን ለብሶ  ባልደረቦቹን ተቀላቀለ፡፡   
ከሁለት ሰዓት በኋላ  ግዳጁን ተወጥቶ፣ ወደ ሠርግ ሥነሥርዓቱ ሲመለስ፤ “እንግዶች በሙሉ ቆመው  በጭብጨባ ተቀብለውታል” ብላለች፤ውድ ባለቤቱ  ክሪስታ ቦላንድ፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር ሠርጋቸውን በዳንስ ያደመቁት፡፡ በጀግንነት ተግባር የታጀበ፣ አይረሴ  ሠርግ  ይሏል ይኼ ነው፡፡      
*   *   *
የአየርላንድ ተወላጇ ካይትሮይና ላሊ፤ ከዱብሊን  ትሪንቲ ኮሌጅ የተመረቀችው የዛሬ 14 ዓመት ነበር፡፡ በ2015  ወደ ኮሌጁ የተመለሰችው ትምህርቷን ለመቀጠል አልነበረም፡፡ በጽዳት ሠራተኛነት ተቀጥራ ለመሥራት እንጂ፡፡ ይሄኔ ነበር “Eggshells”  የተሰኘው የበኩር  ረዥም ልብወለዷ ለንባብ የበቃው፡፡  ይሄን ልብወለዷን የጻፈችው  ከሥራ ውጭ በቆየችባቸው  ዓመታት ነበር፡፡     
 ባለፈው ሳምንት ታዲያ ልታምነው ያዳገታትን  ዜና ሰማች፡፡ “Eggshells”  የተሰኘው  መጽሐፏ የኮሌጁን ከፍተኛ የሥነጽሁፍ ሽልማት አሸነፈ፡፡ ሩኔይ የአየርላንድ ሥነጽሁፍ ሽልማት፤ “የላቀ ተስፋ” ለሚጣልባቸው፣ ዕድሜያቸው  ከ40 ዓመት በታች ለሆኑ ጸሐፍት የሚሰጥ ዓመታዊ ሽልማት ነው፡፡ የሥነጽሁፍ ሽልማቱ 11 ሺ 500 ዶላርም (300 ሺ ብር ገደማ) ይጨምራል፡፡  ሽልማቱን ማሸነፏ “ፍጹም ተዓምር ነው” ያለችው  ላሊ፤ በአሁኑ ወቅት ሁለተኛ ልብወለዷን በመጻፍ ላይ እንደምትገኝ ታውቋል፡፡ ማን ያውቃል፣ ለሁለተኛ  ሽልማት ትበቃ ይሆናል፡፡      
ምንጭ፡- (THE WEEK October 12,2018)

Read 4181 times
Administrator

Latest from Administrator