Sunday, 11 November 2018 00:00

በእንግሊዝ ከ7 ሺህ በላይ ቤተሰቦች አሁንም ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን ያያሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን ፋሽኑ ካለፈበትና ባለቀለም ቴሌቪዥን ከመጣ ከ50 አመታት በላይ ቢሆነውም፣ በእንግሊዝ ከ7 ሺህ በላይ ቤተሰቦች አሁንም ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን እንደሚያዩ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
በእንግሊዝ ባለቀለም ቴሌቪዥን ገበያ ላይ የዋለው እ.ኤ.አ በ1967 እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ በአገሪቱ 7 ሺህ 161 ያህል ቤተሰቦች አሁንም ድረስ ቴሌቪዥናቸውን እንዳልቀየሩ አመልክቷል፡፡ ባለቀለም ቴሌቪዥን ከመጣ በኋላ ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን የሚገዙ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ቢሆንም አንዳንዶች ግን ለመቀየር አለመፈለጋቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 2409 times