Tuesday, 27 November 2018 00:00

ከ9ሚ. ናይጀሪያውያን ነፍሰ-ጡሮች የኤችአይቪ ምርመራ የሚያደርጉት 2.4 ሚ. ብቻ ናቸው

Written by 
Rate this item
(3 votes)


221 ሺህ 772 ናይጀሪያውያን ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ይገኛል

በናይጀሪያ በየአመቱ ከ9 ሚሊዮን በላይ ነፍሰጡር ሴቶች እንደሚኖሩና ከእነዚህም መካከል የኤች አይ ቪ ምርመራ የሚያደርጉት 2.4 ሚሊዮን ያህሉ ብቻ መሆናቸውን የአገሪቱ መንግስት አስታውቋል፡፡
የናይጀሪያ የጤና ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው በአገሪቱ የቅድመ ወሊድ የህክምና አገልግሎት አቅርቦት የሚያገኙት 3.6 ሚሊዮን ያህል ነፍሰጡሮች ብቻ ሲሆኑ፣ ከእነዚህም መካከል የኤች አይ ቪ ምርመራ የሚያደርጉት 2.4 ሚሊዮን ያህሉ ብቻ ናቸው፡፡
በየአመቱ የኤች አይ ቪ ምርመራ ከሚያደርጉት 2.4 ሚሊዮን ያህል የአገሪቱ ሴቶች መካከል በትንሹ 64 ሺህ የሚሆኑት በደማቸው ውስጥ የኤች አይ ቪ ቫይረስ እንደሚገኝባቸው ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ኤች አይ ቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ከሚገን 64 ሺህ ያህል ነፍሰጡሮች መካከል የጸረ ኤች አይቪ ኤድስ መድሃኒት ተጠቃሚ የሚሆኑት 74 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደሆኑ የጠቆመው ሚኒስቴሩ፣ በናይጀሪያ 221 ሺህ 772 ህጻናት ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝ ከእነዚህ መካከልም ህምክና የሚያገኙት 54 ሺህ ያህሉ ብቻ እንደሆኑ አመልክቷል፡፡


Read 4094 times