Saturday, 24 November 2018 13:06

“ለአርቲስቶች ነፃ የትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)


በቢዝነስና ኪነ ጥበብ  ዘርፎች ሥልጠናዎችን እየሰጠ የሚገኘው “ልቀት ቢዝነስ እና አርት ኮሌጅ” ሁኔታዎች ሳይመቻቹላቸውና መክፈል ሳይችሉ ቀርቶ ወደ ኪነ ጥበብ ሙያ ለገቡ አርቲስቶች ነፃ የትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው፡፡ ኮሌጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ ራሱን በማሳደግና አቅሙን በመገንባት፣ ወደ ዩኒቨርሲቲ የማደግ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ ሲሆን ብዙ የቢዝነስና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን እያፈራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የኪነ ጥበቡን ዘርፍ ለማሳደግና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት መክፈል የማይችሉ አርቲስቶችን በነፃ ተቀብሎ ለማስተማር መዘጋጀቱን የኮሌጁ የትምህርት አስተዳደር ኃላፊ ዲን አስታውቀዋል፡፡ የነፃ ትምህርት ዕድሉ መጠቀም የሚፈልጉ ከህዳር 17 እስከ 30/2011 ዓ.ም ባሉት ቀናት አራት ኪሎ ትምህርት ሚኒስቴር ጀርባ በሚገኘው አይሲቲማርት ህንፃ 3ኛ ፎቅ በሚገኘው የኮሌጁ ቢሮ መመዝገብ እንደሚችሉም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡

Read 1203 times