Print this page
Saturday, 22 December 2018 13:06

በአመቱ ከ4 ሺህ በላይ ስደተኞች በጉዞ ላይ ሞተዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በተገባደደው የፈረንጆች አመት 2018 ብቻ በመላው አለም ከ4 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በስደት ጉዞ ላይ እያሉ ለሞት መዳረጋቸውን ተመድ አስታውቋል፡፡ አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ያወጣውን አመታዊ ሪፖርት ጠቅሶ ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፤በአመቱ 4 ሺ 476 የተለያዩ አገራት ዜጎች በስደት ጉዞ ላይ ሳሉ አደጋ፣ ጥቃትና ርሃብን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ለሞት የተዳረጉ ሲሆን ግማሽ ያህሉ ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት ያሰቡ ነበሩ፡፡
ከአለማችን አጠቃላይ ህዝብ 3.4 በመቶ የሚሆነው የኢኮኖሚ ችግር፣ ግጭትና የተፈጥሮ አደጋን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች አገሩን ጥሎ ለመሰደድ እየተገደደ ነው ያለው ድርጅቱ፣ በአመቱ ከ110 ሺህ በላይ የተለያዩ አገራት ስደተኞች ወደ አውሮፓ አገራት መሰደዳቸውን አመልክቷል፡፡


Read 898 times
Administrator

Latest from Administrator