Print this page
Tuesday, 01 January 2019 00:00

የአለማችን ቢሊየነሮች ትርፍና ኪሳራ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የአለማችን ቢሊየነሮች ትርፍና ኪሳራ
የእንግሊዝን ከአውሮፓ ህብረት የመውጣት ዕቅድና በአሜሪካና በቻይና መካከል የተፈጠረውን የንግድ ጦርነት ጨምሮ የአለማችን የአክሲዮን ገበያ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት በቀውስ ውስጥ ሆኖ የከረመበትና ስመጥር ኩባንያዎችና ቢሊየነሮች የከፋ ኪሳራን ያስተናገዱበት አመት ነበር - 2018፡፡
የአለማችን ቢሊየነሮች በአመቱ በድምሩ 511 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ እንደከሰሩ የዘገበው ፎርብስ፣ እጅግ ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰበት በ12 ወራት ጊዜ ውስጥ 18.7 ቢሊዮን ዶላር ያጣው የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙክበርግ ነው ብሏል፡፡ 16.2 ቢሊዮን ዶላር የሚገመተውን የአመቱ ሁለተኛው ከፍተኛ ኪሳራ ያስተናገደው የአለማችን ባለጸጋ፣ ኢንዲቴክስ የተባለው የአልባሳት አምራች ኩባንያ ባለቤት የሆነው አማኒኮ ኦርቴጋ ነው፡፡
ለዙክበርግ ከፍተኛው የኪሳራ አመት ሆኖ ያለፈው 2018፣ የሃብት መጠኑን በ27.9 ቢሊዮን ዶላር ለጨመረው የአማዞኑ መስራች ጄፍ ቤዞስ በአንጻሩ፣ ከፍተኛ የትርፍ ዓመት ነበር ተብሏል፡፡ በፋሽን ኢንዱስትሪው መስክ የተሰማራው ዩኒሎ ኩባንያ መስራችና ባለቤት ጃፓናዊው ቢሊየነር ታዳሺ ያኒ በ7 ቢሊዮን ዶላር፣ ቫጊት አሌክፔሮቭ በ4.6 ቢሊዮን ዶላር የሃብት መጠናቸውን በመጨመር ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አመቱን በስኬት እያጠናቀቁ መሆኑ  ተነግሯል፡፡


Read 4134 times
Administrator

Latest from Administrator