Sunday, 06 January 2019 00:00

ዚምባቡዌ 16 ሺህ ስራ አጥ የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን ወደ ደቡብ ሱዳን ትልካለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የዚምባዌ መንግስት ከዩኒቨርሲቲ ቢመረቁም ስራ ሊያገኙ ያልቻሉ ከ16 ሺህ በላይ የአገሪቱ ዜጎችን በቅርቡ ወደ ደቡብ ሱዳን ለመላክ ማቀዱን ሳውዝ ሱዳን ኒውስ ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡
የዚምባቡዌ የከፍተኛ ትምህርት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ፕሮፌሰር አሞን ሙሪዋን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ አገሪቱ በርካታ ቁጥር ያላቸው ምሩቃንን ወደ ደቡብ ሱዳን በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የሚያስችላትን የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ነው፡፡
ዚምባቡዌ በአዲሱ የፈረንጆች አመት 2019 ብቻ በተለያዩ የሙያ መስኮች ከዩኒቨርስቲዎች የተመረቁና ስራ ያልያዙ ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ደቡብ ሱዳን ለመላክ ማቀዷን የጠቆመው ዘገባው፣ ታዋቂ የዚምባቡዌ ጋዜጠኞች ግን በርካታ ቁጥር ያላቸውን የራሷን የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ስራ ማስያዝ ያልቻለችው ደቡብ ሱዳን ከዚምባቡዌ ምሁራንን ማስገባቷ አስቂኝ ነው ሲሉ መተቸታቸውን አመልክቷል፡፡

Read 1020 times