Print this page
Sunday, 06 January 2019 00:00

በአዲሱ ዓመት ከ395 ሺህ በላይ ህጻናት ተወልደዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የፈረንጆች አመት 2019 የመጀመሪያዋ ቀን በሆነቺው ባለፈው ማክሰኞ ብቻ በመላው አለም ከ395 ሺህ በላይ ህጻናት ተወልደዋል ተብሎ እንደሚገመት የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡
ከአለማችን አገራት መካከል ጃኑዋሪ 1 ቀን 2019 ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህጻናት የተወለዱባት ቀዳሚዋ አገር ህንድ ናት ያለው ድርጅቱ፣ በዕለቱ 69 ሺህ 944 ህንዳውያን ህጻናት ወደዚህች አለም መምጣታቸውን አመልክቷል፡፡ በዕለቱ 44 ሺህ 940 ህጻናት የተወለዱባት ቻይና በሁለተኛነት ስትከተል፣ ናይጀሪያ በ25 ሺህ 685 ህጻናት የሶስተኛነት ደረጃን መያዟንም ድርጅቱ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
ፓኪስታን በ15 ሺህ 112፣ ኢንዶኔዢያ በ13 ሺህ 256፣ አሜሪካ በ11 ሺህ 86፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ10 ሺህ 53፣ ባንግላዴሽ በ8 ሺህ 428 ህጻናት በቅደም ተከተላቸው መሰረት እስከ ስምንተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውን የገለጸው ድርጅቱ፣ በዕለቱ ከተወለዱት የአለማችን ህጻናት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በስምንቱ አገራት ውስጥ እንደተወለዱም አመልክቷል፡፡

Read 988 times
Administrator

Latest from Administrator