Saturday, 05 January 2019 00:00

የገና ኮንሰርት በደብረ ማርቆስ ከተማ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አማን አድቨርታይዚንግ ከደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “የገና ኮንሰርት” የሙዚቃ ድግስ ነገ በዋዜማው በደብረ ማርቆስ ከተማ ይካሄዳል፡፡
አዘጋጆቹ በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በኮንሰርቱ ላይ ድምጻዊ እሱባለው ይታየው (የሺ)፣ ቃቆ ጌታቸው፣ አንተነህ ተስፋዬና ሙሉአለም ጌታቸው የሚያቀነቅኑ ሲሆን ዲጄ ቤቢም በተለያዩ ጥዑመ ዜማዎች ኮንሰርቱን ያደምቀዋል ተብሏል፡፡
በኮንሰርቱ ላይ ለመታደም መደበኛው ትኬት 100 ብር፣ ለጥንዶች 150 ብር እየተሸጠ ሲሆን ትኬቶቹን፣ በኤልቤት ካፌ፣ በካሚሊያ ካፌ፣ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ በንጉስ ተ/ሃይማኖት አደባባይና በሀዲስ ዓለማየሁ አደባባይ ማግኘት እንደሚቻል የአማን አድቨርታይዚንግ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ፣ ወጣት አማኑኤል የሺወንድ አስታውቋል፡፡  

Read 716 times