Saturday, 19 January 2019 00:00

የአለማቀፍ ብድር መጠን 244 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አለማቀፉ የብድር መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ 244 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱንና ይህም መጠን ከአጠቃላዩ አለማችን ኢኮኖሚ ከሶስት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ መነገሩን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
ኢንስቲቲዩት ኦፍ ኢንተርናሽናል ፋይናንስ የተባለው ተቋም ባለፈው ማክሰኞ ይፋ ያደረገውን አለማቀፍ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአለማቀፍ ደረጃ የብድር መጠን ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት በ318 በመቶ ብልጫ ይዞ ይገኛል፡፡
የአለማችን አጠቃላይ ብድር በ2018 የመጀመሪያዎቹ ወራት 247.7 ትሪሊዮን ዶላር በመድረስ ክብረወሰን አስመዝግቦ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ በሶስተኛው ሩብ አመት ወደ 244 ትሪሊዮን ዶላር ዝቅ ካለው አጠቃላይ አለማቀፍ ብድር ውስጥ 65 ትሪሊዮን ያህሉ የመንግስት ብድር ሲሆን፣ 72 ትሪሊዮን ያህሉ ደግሞ ፋይናንስ ነክ ያልሆኑ ኩባንያዎች ብድር ነው ብሏል፡፡
የብድር ወለድ መጠን በአለማቀፍ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ተከትሎ አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም አይኤምኤፍ በቅርቡ ባወጣው መግለጫ፣ መንግስታት የሚወስዱትን ብድር በመመጠን እያደገ የመጣውን አለማቀፍ ብድር ለመግታት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱና  በዕዳ ጫና ከሚመጣ ቀውስ ለመዳን የሚያስችሉ ስራዎችን እንዲያከናውኑ ጥሪ ማቅረቡንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1020 times