የአለማችን ቁጥር አንድ የሞባይል ስልኮች አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ፣ በመጪው መጋቢት ወር በገበያ ላይ ያውለዋል ተብሎ የሚጠበቀው “ጋላክሲ ኤስ10” ስማርት ፎን 1ሺህ 400 የእንግሊዝ ፓውንድ የመሸጫ ዋጋ እንደተተመነለት ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
“ጋላክሲ ኤስ10” በተለያዩ 3 ቀለሞችና መጠኖች እንዲሁም በተለያየ የመሸጫ ዋጋ ለገበያ ይቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆመው ዘገባው፤ ዝቅተኛው የመሸጫ ዋጋው 779 ፓውንድ፣ ከፍተኛው ደግሞ 1ሺህ 400 ፓውንድ ዶላር እንደሚሆን ገልጧል፡፡
በደቡብ ኮርያው የኤሌክትሮኒክስ አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ ተመርቶ በጥቁር፣ ነጭና አረንጓዴ ቀለሞች ለገበያ ይቀርባል የተባለውና ከነባሮቹ የጋላክሲ ሞባይሎች የተለየና የተሻለ እንደሆነ የተነገረለት “ጋላክሲ ኤስ10”፤ በመጪው ወር መጨረሻ ላይ ለንደን ውስጥ በሚከናወን የምረቃ ስነስርዓት ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ለእይታ ይበቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ