Print this page
Tuesday, 05 February 2019 00:00

በሜዲትራንያን ባህር በየቀኑ 6 ስደተኞች እንደሞቱ ተመድ አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018፣ የሜዲትራንያን ባህርን አቋርጠው ወደተለያዩ የአውሮፓ አገራት ለመግባት ጉዞ ከሚያደርጉ ስደተኞች መካከል በየቀኑ በአማካይ ስድስቱ ለሞት እንደተዳረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እንዳለው፣ በ2018 ብቻ 2 ሺህ 275 የተለያዩ አገራት ስደተኞች ሜዲትራንያን ባህርን አቋርጠው በመጓዝ ላይ እያሉ ለሞት ተዳርገዋል፡፡
በተያያዘ ዜና ደግሞ ባለፈው ማክሰኞ በጅቡቲ የቀይ ባህር ዳርቻ በርካታ ቁጥር ያላቸው ስደተኞችን አሳፍረው በመጓዝ ላይ የነበሩ ሁለት ጀልባዎች ሰጥመው 130 ያህል ስደተኞች ሳይሞቱ እንዳልቀሩ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡

Read 2365 times
Administrator

Latest from Administrator