Print this page
Saturday, 09 February 2019 13:14

“አጥራችን ኢትዮጵያ ናት፤ ሌላ አጥር የለንም” አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ጦቢያ ግጥም በጃዝ መንደር በአገሪቱ በሚገኙ 45ቱም ዩኒቨርሲቲዎች በመዘዋወር “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማድመቅ” በሚል መርህ ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ጋር ለመወያየትና የተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችን ለማቅረብ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር ውል ፈፅሟል፡፡
በዚህ መሰረትም በአዲስ አበባና በወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሮግራሙ የተካሄደ ሲሆን በቀጣይም እስከመጪው የክረምት ወራት መግቢያ ድረስ በ20 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሮግራሙን ለማካሄድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የፕሮግራሙ አስተባባሪ ገጣሚ ምስራቅ ተረፈ ለአዲስ አድማስ ተናግራለች፡፡ በአዲስ አበባና በወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲዎቹ ተማሪዎችና መምህራን “አጥራችን ኢትዮጵያ ናት፤ ሌላ አጥር የለንም” የሚል ቃል ኪዳን ስነ ስርዓት አካሂደዋል፡፡

Read 1220 times
Administrator

Latest from Administrator