ወርሃዊው “ቃልና ቀለም” ሁለተኛ ዙር የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ማክሰኞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በዋቢሸበሌ ሆቴል እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡
ባለሙያዎች በምሽቱ በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር ዲስኩር፣ ገጣሚዎቹ የሻው ተሰማ (የኮተቤው)፣ ደራሲ ህይወት እምሻው፣ ዘላለም ምህረቱ፣ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ፣ ሙዚቀኛ ዘቢብ ግርማ፣ ገጣሚ ልሳን ሀጎስ ገጣሚ ምስክር ይብራ፣ ገጣሚ ዳግም ህይወትና እዮብ ሙሴ ሥራዎቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን በተስፋሁን ከበደ የአንድ ሰው ተውኔት እንደሚቀርብና ዝግጅቱ በመሶብ ባህላዊ ባንድ እንደሚታጀብ ታውቋል፡፡ የመግቢያ ዋጋው 100 ብር ሲሆን መድረኩ በተወዳጅ እሸቱና መቅደላ መኩሪያ እንደሚመራም አዘጋጆቹ ታውቋል፡፡
Saturday, 16 February 2019 15:05
“ቃልና ቀለም” የኪነ ጥበብ ምሽት ማክሰኞ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና