Print this page
Tuesday, 26 February 2019 15:10

የጃፓኑ ጠ/ሚ ትራምፕን ለኖቤል የሰላም ሽልማት ያጨሁት ተገድጄ ነው አሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)


የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ፣ የአሜሪካውን አቻቸውን ዶናልድ ትራምፕን ለኖቤል የሰላም ሽልማት ማጨታቸውንና ይህንን ያደረጉትም በትራምፕ አስተዳደር በተደረገባቸው ጫና እንጂ በራሳቸው ተነሳሽነት አለመሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ከወራት በፊት ከዶናልድ
ትራምፕ አስተዳደር በተላከላቸው ደብዳቤ፣ ትራምፕን ለኖቤልየሰላም ሽልማት እንዲያጩ በተጠየቁት መሰረት፣ ያለ ፍላጎታቸው
ትራምፕን ማጨታቸወን አሻይ የተባለው የጃፓን ጋዜጣ ከሰሞኑ ያስነበበውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው አስታውቋል፡፡ ጋዜጣው መረጃውን ይፋ ያደረገው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ለኖቤል ሽልማት አጭተውኛል በሚል ባለፈው ሳምንት በዋይት ሃውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በኩራት መነገራቸውን ተከትሎ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ የትራምፕ አስተዳደር በሽንዞ አቤ ላይ ጫና ማድረጉን በተመለከተ የሰጠው ምላሽ አለመኖሩን አመልክቷል፡፡

Read 1969 times
Administrator

Latest from Administrator