Print this page
Sunday, 03 March 2019 00:00

ቢሊየነሩ ጆፍ ቤዞስ፣በልግስናም የአለማችን ቁንጮ ሆነዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የወቅቱ የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆኑት አሜሪካዊው ቢሊየነር ጄፍ ቤዞስ በአመቱ ከፍተኛ ገንዘብ ለበጎ አድራጎት ተግባራት በመለገስ በአለማችን በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸው ተዘግቧል፡፡
የአማዞን ኩባንያ መስራቹ ጄፍ ቤዞስ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018 ብቻ ከባለቤታቸው ጋር ባቋቋሙት ቤዞስ ዴይ ዋን ፈንድ በተባለው ድርጅት በኩል ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች 2 ቢሊዮን ዶላር መለገሳቸውንና በክሮኒክል ኦፍ ፌላንትሮፒ ተቋም የአመቱ ምርጥ 50 ለጋሾች ዝርዝር ውስጥ በቀዳሚነት መቀመጣቸው ተነግሯል፡፡
ለኪነጥበብ፣ ትምህርት፣ ጤናና ሌሎች ዘርፎች 767 ሚሊዮን ዶላር የለገሱትና በሚዲያና መዝናኛው መስክ ስኬታማ ለመሆን የቻሉት ማይክል ብሉምበርግ፣ በአመቱ ምርጥ 50 ለጋሾች ዝርዝር ውስጥ የሁለተኛነት ደረጃን የያዙ ሲሆን፣ የኢቤይ ኩባንያ መስራቾቹ ጥንዶቹ ፔሪ እና ፓም ኦሚዲያር 392 ሚሊዮን ዶላር በመለገስ በሶስተኛነት ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
በምርጥ ለጋሾች ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ሌሎች ታዋቂ ሰዎች መካከል 213.56 ሚሊዮን ዶላር በመለገስ በሰባተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት የፌስቡኩ መስራች ማርክ ዙከርበርግና ባለቤቱ ፕሪሲሊካ ቻን ይገኙበታል፡፡




Read 1118 times
Administrator

Latest from Administrator