Wednesday, 13 March 2019 00:00

የአለማችን እጅግ ውድ መኪና በ18.9 ዶላር ተሸጠች

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ታዋቂው የፈረንሳይ የመኪና አምራች ኩባንያ ቡጋቲ የተመሰረተበትን 110ኛ አመት ምክንያት በማድረግ በልዩ ሁኔታ ያመረታትና ላ ቮይቸር ኖይር የሚል ስያሜ የተሰጣት የአለማችን እጅግ ውድ መኪና በ18.9 ሚሊዮን ዶላር መሸጧን ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡
ባለፈው በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በስዊዘርላንድ በተከፈተው የጄኔቫ አለማቀፍ የሞተር አውደርዕይ ላይ ለጀመሪያ ጊዜ ይፋ የተደረገችውንና በልዩ ሁኔታ የተመረተችውን ይህችን ዘመናዊ የቅንጦት መኪና ይህን ያህል ገንዘብ ከፍሎ የገዛው ግለሰብ ወይም ተቋም ማንነት ለጊዜው ይፋ አለመደረጉን ዘገባው ገልጧል፡፡
የኩባንያው ፕሬዚደንት ስቴፋን ዊንኬልማን እጅግ የላቀ ቴክኖሎጂ፣ ወደር የለሽ ምቾትና ፍጹም ውበትን አጣምራ የያዘች የምንኮራባት ምርታችን ሲሉ በአድናቆት ያንቆለጳጰሷት  ጥቁር ቀለም ያላት ላ ቮይቸር ኖይር ባለ 16 ሲሊንደር ስትሆን 1 ሺህ 500 የፈረስ ጉልበት እንዳላትም ዘገባው አመልክቷል፡፡
መኪናዋ አንድ ለእናቱ እንደሆነችና ዳግም ተመርታ ለሌለ ሰው እንደማትሸጥ የጠዎመው ዘገባው፣ እ.ኤ.አ በ1909 የተመሰረተው የፈረንሳዩ የመኪና አምራች ኩባንያ ቡጋቲ በጀርመኑ ቮልስዋንገን ባለቤትነት እየተዳደረ እንደሚገኝም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 4857 times