በፍልስፍና መምህሩ ብሩህ አለምነህ የተሰኘ “ፍልስፍና 3” መጽሐፍ ላይ የዛሬ ሳምንት ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ-መፃሕፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡ በዕለቱ በመጽሐፉ 3 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል የተባለ ሲሆን ርዕሶቹም “ቅኔና ፍልስፍና” በመጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር፣ “ሀይማኖትና ዘመናዊነት” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህሩ በአቶ ፋሲል መርሃዊ እንዲሁም “ሰሞነ ህማማትና የኢትዮጵያ ሙዚቃ”
በመሪጌታ ፅጌ መዝገቡ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡ ፍላጐት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ አዘጋጅ ዘንባባ የማስታወቂያ ድርጅት ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና