Print this page
Saturday, 06 April 2019 15:54

ኬንያ፤ ተመድ አልሻባብን በገንዘብ ይደግፋል ስትል ወቀሰች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዱቤ ባለመክፈላቸው ሆስፒታል ውስጥ የታሰሩ 258 ኬንያውያን ተፈቱ

         የኬንያ መንግስት በሶማሊያ ለሚንቀሳቀሰው አሸባሪው ቡድን አልሻባብ በሚሊዮኖች ዶላር የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል ስትል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን መውቀሱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና ጸሃፊ ማቻሪያ ካሙ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ በሶማሊያ በአሸባሪ ቡድኖች በተያዙ አካባቢዎች እርዳታ ለመስጠት እንዲችል ቡድኖቹ መንገድ እንዲከፍቱለት ለማድረግ ለሰብዓዊ ድጋፍ ከታሰበው እርዳታ ውስጥ 10 በመቶ ያህሉን ለአሸባሪዎች ይሰጥ ነበር ሲሉ ትችታቸውን መሰንዘራቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ተመድ በሶማሊያ ለሚንቀሳቀሰው አልሻባብ 12 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ በመደለያነት መስጠቱን የሚናገሩት ማቻሪያ፤ ተመድ ለአሸባሪ ቡድኖች በመደለያ መልክ ገንዘብ መክፈሉን እንዲያቆም ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ማቻሪያ ያቀረቡት ውንጀላ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ ተቃውሞ ይገጥመዋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የህክምና አገልግሎት ክፍያቸውን አልፈጸሙም በሚል በኬንያታ ብሄራዊ ሆስፒታል ታስረው የቆዩ 258 ታማሚዎች ባለፈው ማክሰኞ ከእስር መፈታታቸውን ስታንዳርድ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡በሆስፒታሉ የተለያዩ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎቶችን በዱቤ ካገኙ ታካሚዎች መካከል 30 በመቶ ያህሉ ክፍያቸውን ባለመፈጸማቸው በሆስፒታሉ ውስጥ እስከ አራት ወራት ለሚደርስ ጊዜ ታስረው እንደቆዩ ያስታወሰው ዘገባው፣ የታካሚዎቹ ቤተሰቦችና የመብት ተሟጋቾች ድርጊቱን በስፋት መቃወማቸውንና ጫና ማሳደራቸውን ተከትሎ ሊፈቱ መቻላቸውንም አመልክቷል፡፡

Read 1317 times
Administrator

Latest from Administrator