Print this page
Saturday, 06 April 2019 15:56

ኢቫንካ ትራምፕ ኢትዮጵያንና አይቬሪኮስትን ልትጎበኝ ነው

Written by 
Rate this item
(5 votes)

 የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልጅናየዋይት ሃውስ አማካሪዋ ኢቫንካ ትራምፕ ከሳምንታት በኋላ ኢትዮጵያንና አይቬሪኮስትን እንደምትጎበኝ መነገሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ዋይት ሃውስ ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፤ በሁለቱ አገራት የአራት ቀናት ቆይታ የምታደርገው ኢቫንካ ትራምፕ፤ በአይቬሪኮስት በሚካሄደው የሴቶች ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጎልበት ጉባኤ ላይ የምትሳተፍ ሲሆን፣ በአገራቱ ከፖለቲካ መሪዎችና ከሴት ስራ ፈጣሪዎች ጋር ውይይት ታደርጋለች፡፡
ባለፈው የካቲት ወር ላይ የተጀመረውና በኢቫንካ ትራምፕ የሚመራው ውሜንስ ግሎባል ዲቨሎፕመንት ኤንድ ፕሮስፐሪቲ ኢኒሽየቲቭ እስከ 2025 የፈረንጆች አመት ድረስ ባላደጉ አገራት ውስጥ የሚገኙ 50 ሚሊዮን ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም የመገንባት ግብ ማስቀመጡንና የኢቫንካ ጉብኝትም የዚህ ፕሮግራም አካል መሆኑን ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 7154 times
Administrator

Latest from Administrator