Monday, 15 April 2019 00:00

ዙማ ከጋዳፊ 30 ሚ. ዶላር ተቀብለዋል መባሉን አስተባበሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አድርገውት ከሆነ በእድሜ ልክ እስራት ሊቀጡ ይችላሉ

             የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ፣ ከሟቹ የሊቢያው አቻቸው ሙአመር ጋዳፊ 30 ሚሊዮን ዶላር  ተቀብለዋል በሚል ከሰሞኑ የወጣውን ዘገባ ፍጹም ውሸት ነው ሲሉ በትዊተር ገጻቸው ማስተባበላቸው ተዘግቧል፡፡
ሰንደይ ታይምስ ሰሞኑን ባወጣው ዘገባው፤ ጃኮብ ዙማ ከጋዳፊ ብዙ ገንዘብ ተቀብለዋል፤ በህገወጥ መንገድ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ከሊቢያ ወደ ደቡብ አፍሪካ አሸሽተዋል ማለቱን ተከትሎ፣ ጉዳዩ መነጋገሪያ ሆኖ መሰንበቱን የገለጸው ቢዝነስ ኢንሳይደር፣ በእርግጥም አድርገውት ከሆነ በእድሜ ልክ እስራት ሊቀጡ እንደሚችሉ መነገሩን ጠቁሟል፡፡
ጃኩብ ዙማ ከስምንት አመታት በፊት የሞቱትን ጋዳፊን በህይወት እያሉ ለመጨረሻ ጊዜ በአካል ያገኙ መሪ እንደነበሩ ያስታወሰው ዘገባው፤ በወቅቱም ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ከሊቢያ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማሸሽ ሳያሴሩና ተግባራዊ ሳያደርጉት እንዳልቀሩ መነገሩን አመልክቷል፡፡
የደቡብ አፍሪካ የደህንነት ባለሙያዎች ጃኩብ ዙማ ከጋዳፊ 30 ሚሊዮን ዶላር መቀበላቸውን የሚያመለክት መረጃ እንዳገኙ ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት ራሞፋሳ ጥቆማ መስጠታቸውንና በጉዳዩ ዙሪያ ምርመራ ሳይጀመር እንዳልቀረም ሰንደይ ታይምስ ባወጣው ዘገባ ገልጧል፡፡

Read 5151 times