ላለፉት 5 ዓመታት በስልጣን ሹክቻ ውስጥ ሆነው እጅግ በርካታ ደቡብ ሱዳንያውያንን ለሞትና ለስደት ባበቁት የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኬርና በቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት ሪክማቸር መካከል ሰላም እንዲሰፍንና ተፋላሚዎቹ ግጭታቸውን አቁመው ህዝቡን ከሞት፣ ከስደትና ከመከራ እንዲታደጉና ሰላም እንዲያሰፍኑ በሁለቱ መሪዎች እግር ስር ወድቀው ጫማቸውን በመሳም የተማፀኑት የሮማው ሊቀጳጳስ ፍራንሲስ የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በደቡባዊ ሮማ በሚገኘው ቬልተሪ እስር ቤት በመሄድ የ12 እስረኞችን እግር አጥበው መሳማቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡