Print this page
Monday, 06 May 2019 12:37

የ2019 ቢልቦርድ የሙዚቃ ሽልማት ተከናወነ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከአለማችን ታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች አንዱ የሆነው የቢልቦርድ የሙዚቃ ሽልማት ባለፈው ረቡዕ ምሽት በላስ ቬጋስ በደማቅ ስነስርዓት የተከናወነ ሲሆን በምርጥ አርቲስት ዘርፍ ታዋቂው ራፐር ድሬክ አሸናፊ ሆኗል፡፡
በምርጥ ሴት አርቲስት ዘርፍ አሪያና ግራንዴ አሸናፊ ስትሆን፣ በምርጥ ካንትሪ አርቲስት ዘርፍ ሉክ ኮምብስ፣ በምርጥ ሮክ አርቲስት ዘርፍ ኢማጂን ድራጎንስ ለሽልማት በቅተዋል፡፡
በዘንድሮው የቢልቦርድ ሽልማት ምርጥ አርቲስትን ጨምሮ በተለያዩ 12 ዘርፎች ተሸላሚ የሆነውና አጠቃላይ ያገኛቸውን የቢልቦርድ ሽልማቶች ቁጥር 27 ያደረሰው ታዋቂው ድምጻዊ ድሬክ፣ በቢልቦርድ ታሪክ ብዛት ያላቸው ሽልማቶችን በማግኘት ታሪክ ሰርቷል፡፡ ታዋቂዋ ድምጻዊት ካርዲ ቢ፣ በ21 ዘርፎች ታጭታ የነበረ ቢሆንም፣ በ12 ዘርፎች ለማሸነፍ መቻሏ ተነግሯል፡፡
ቴለር ስዊፍት “ሚ” የተሰኘ የሙዚቃ ስራዋን በማቀንቀን በከፈተችው የዘንድሮው ቢልቦርድ የሙዚቃ ሽልማት ላይ ማሪያ ኬሪ፣ አርያና ግራንዴና ማዶናን ጨምሮ የዓለማችን ኮከብ ድምጻውያን ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን የመድረኩ መሪም ኬሌ ካርልሰን ነበር፡፡

Read 1386 times
Administrator

Latest from Administrator