Monday, 06 May 2019 12:43

የማንዴላ የእስር ቤት ስዕል በጨረታ ሊሸጥ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

       የጸረ አፓርታይድ ታጋዩ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ፣ በእስር ቤት እያሉ የሳሉት ስዕል ኒው ዮርክ ውስጥ ለጨረታ ሊቀርብ መሆኑን የዘገበው ቢቢሲ፤ 90 ሺህ ዶላር ይሸጣል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁሟል፡፡ “ዘ ሴል ዶር” የተሰኘውና ማንዴላ ለ18 አመታት በቆዩበት የሮቢን ደሴት እስር ቤት ውስጥ ሳሉ እንደሳሉት የተነገረለትን ይህን ስዕል ቦንሃማስ በተባለው አጫራች ኩባንያ አማካይነት ለጨረታ የምታቀርበው ፑማላ ማካዚዌ ማንዴላ የተባለችው ልጃቸው እንደሆነች ተነግሯል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ በእስር ቤት በቆዩባቸው 27 አመታትና ከተፈቱ በኋላ የተለያዩ ስእሎችን መሳላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ማንዴላ በድምሩ 25 ያህል ስዕሎችን ሳይስሉ እንዳልቀረ መነገሩን አመልክቷል፡፡

Read 1154 times