በዚህ መሰረት በአዲስ መልክ በተመሰረተው የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር በስራ አስፈፃሚነት የሚሰሩ ሰባት አባላት ተመርጠዋል፡፡ የአዲሱ የኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው የኢቲቪ ስፖርት ክፍል ባልደረባ ዮናስ ተሾመ ሲሆን ምክትል ፕሬዝዳንት የኢንተር ስፖርት ማኔጂንግ ዲያሬክተርና የስፖርት 365 ሬድዮ ቶክሾው አቅራቢ ሁሴን አብዱልቀኒ፤ ዋና ፀሃፊ የኢትዮ ስፖርት ማኔጂግ ዲያሬክተርና የኳስ ሜዳ ኮሜንታተር መንሱር አብዱልቀኒ እንዲሁም በገንዘብ ያዥነት የኤፍም አዲስ 96.3 ስፖርት አዘጋጅ አምሃ ፍሰሃ ሲሾሙ በኦዲተርነት የኢቢኤስ ባልደረባ የሆነው ዘርዓይ እያሱ እና የኢንተር ስፖርት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ብዙአየሁ ዋጋው ተመርጠዋል፡፡