Print this page
Saturday, 08 June 2019 00:00

ለግማሽ ያህሉ አፍሪካውያን ህጻናት ሞት ምክንያቱ ረሃብ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በመላው አፍሪካ 60 ሚሊዮን ያህል ህጻናት የምግብ አቅርቦት እንደማያገኙና በአህጉሪቱ በየአመቱ ለሞት ከሚዳረጉ ህጻናት መካከል ግማሽ ያህሉ በርሃብ ምክንያት እንደሚሞቱ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
አፍሪካን ቻይልድ ፖሊሲ የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው ጥናት እንደሚለው፤ ምንም እንኳን የአፍሪካ አገራት በቀርብ አመታት ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ቢያስመዘግቡም፣ ከሶስት አፍሪካውያን ህጻናት አንዱ የመቀንጨር ችግር ተጠቂ ነው፡፡
በመላው አለም በምግብ እጥረት ምክንያት በየቀኑ 10 ሺህ ያህል ህጻናት ለሞት እንደሚዳረጉ የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤ የህጻናት ረሃብ በአለማቀፍ ደረጃ መሻሻል ቢያሳይም በአንዳንድ የአፍሪካ አገራት ግን ችግሩ በእጅጉ እየተባባሰ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡
90 በመቶ አፍሪካውያን ህጻናት የአለም የጤና ድርጅት ያስቀመጠውን ዝቅተኛ የምግብ ንጥረነገር ቅንብር ደረጃ ያላሟሉ መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ከአምስት አፍሪካውያን ህጻናት መካከል ሁለቱ በቋሚነት ምግብ እንደማይመገቡ ገልጧል፡፡

Read 912 times
Administrator

Latest from Administrator