Saturday, 08 June 2019 00:00

ሪሃና በ600 ሚ. ዶላር የአለማችን እጅግ ባለጸጋ ሴት ሙዚቀኛ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አጠቃላይ የሀብቷ መጠን 600 ሚሊዮን ዶላር እንደደረሰ የሚነገርላት አሜሪካዊቷ ድምጻዊት ሪሃና፣ በታዋቂው የፎርብስ መጽሄት፣ የአለማችን ሴት ሙዚቀኞች የሀብት ደረጃ በመሪነት መቀመጧ ተነግሯል፡፡
ሪሃና ከሙዚቃ ስራዎቿ፣ ከኮንሰርት በተጨማሪ ታዋቂውን ፌንቲ ቢዩቲ ኩባንያ ጨምሮ ባቋቋመቻቸው የፋሽንና የውበት ኩባንያዎች ከፍተኛ ገቢ እንደምታገኝ የጠቆመው ፎርብስ፤ ከፍተኛውን የ570 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘችውም ከፌንቲ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በዘንድሮው የፎርብስ መጽሄት የአለማችን ሴት ባለጸጋ ሙዚቀኞች ዝርዝር ውስጥ የሁለተኛነት ደረጃን የያዘቺው ሌላኛዋ ታዋቂ ድምጻዊት ማዶና ስትሆን፣ ድምጻዊቷ 570 ሚሊዮን ዶላር ሃብት እንዳላት ፎርብስ አስታውቋል፡፡
ሴሊን ዲዮን በ450 ሚሊዮን ዶላር፣ ቢዮንሴ ኖውልስና ባርባራ ስቴሪሳንድ በ400 ሚሊዮን ዶላር፣ ቴለር ስዊፍት በ360 ሚሊዮን ዶላር እንደ ቅደም ተከተላቸው ከሶስተኛ እስከ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ የያዙ ሌሎቹ የአለማችን ዝነኛ ድምጻውያን መሆናቸውንም ፎርብስ መጽሄት ሰሞኑን ባወጣው መረጃ አመልክቷል፡፡

Read 1046 times