በዳሪክ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን በየወሩ በተለያዩ ሚዲያ ነክ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚካሄደው ውይይት የሰኔ ወር መርሃ ግብር “ምርጫና ሚዲያ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ማክሰኞ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በዳይመንድ ሆቴል ይካሄል፡፡
በዕለቱ ምርጫና ሚዲያ በኢትዮጵያ ምን መልክ እንደነበረውና ወደፊት ምን ሊመስል እንደሚገባው በባለሙያዎች ውይይት የሚደረግበት ሲሆን በዕለቱ የመዝናኛ የድንገቴ እንግዳ፣ ሙያዊ ወግ እና ልዩ ልዩ መስተንግዶዎች እንደሚኖሩ የፕሮግራሙ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ማናዬ እውነቱ ገልጿል፡፡
ዳጉ የሚዲያ ውይይትና ሽልማት ፕሮግራም በየወሩ ከሚያካሂደው የሚዲያ ውይይት በተጨማሪ በዓመቱ መጨረሻ ለሚዲያ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ ግለሰቦችና ተቋማትን የሚሸልምበት የሽልማት ሥነ ሥርዓት ይኖረዋል ተብሏል፡፡