Saturday, 08 June 2019 00:00

በ“የአመፃ ልጅ” መፅሀፍ ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


            ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ “Born a crime” በተሰኘውና በጥላሁን ግርማ “የአመፃ ልጅ” በሚል ወደ አማርኛ በተመለሰው መፅሀፍ ላይ በብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የገቨርናንስና ዴቨሎፕመንት ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት መኮንን መንገሻ ሲሆኑ የመፅሀፉ ተርጓሚ ጥላሁን ግርማ በዕለቱ ተገኝተው በውይይቱ ላይ እንደሚካፈሉና የውይይቱ መድረክ በሰለሞን ተሰማ ጂ. እንደሚመራ የገለፀው ሚዩዚክ ሜይ ዴይ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ጋብዟል፡፡

Read 5897 times