Tuesday, 25 June 2019 00:00

በ2018 በአለማችን 71 ሚሊዮን ሰዎች ተፈናቅለዋል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በመላው አለም ጦርነትንና የእርስ በእርስ ግጭትን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሳቢያ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ባለፈው የፈረንጆች አመት 2018 መጨረሻ ላይ 71 ሚሊዮን ያህል መድረሱንና አመቱ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ ከፍተኛው የተፈናቃዮች ቁጥር የተመዘገበበት መሆኑን ተመድ አስታውቋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ባለፈው ረቡዕ ይፋ ባደረገው አለማቀፍ ሪፖርት እንዳለው፣ በአመቱ ከተፈናቀሉት 71 ሚሊዮን ሰዎች መካከል 41.3 ሚሊዮን ያህሉ በአገር ውስጥ የተፈናቀሉ፣ 25.9 ሚሊዮን የሚሆኑት ስደተኞች እንዲሁም 3.5 ሚሊዮን ያህሉ ጥገኝነት ፈላጊዎች ናቸው፡፡
በፈረንጆች አመት 2018 የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር አምና ከነበረው በ2.3 ሚሊዮን ጨምሯል  ያለው ሪፖርቱ፤ የተፈናቀሉት ሰዎች የአንድ አገር ዜጎች ቢሆኑ ከአለማችን አገራት በህዝብ ብዛት 20ኛ ደረጃ ላይ ሊቀመጡ እንደሚችሉ አመልክቷል፡፡
በአዳዲስ ተፈናቃዮች ቁጥር ቀዳሚውን ስፍራ የያዘችው ኢትዮጵያ እንደሆነች የጠቆመው ዘገባው፣ በአመቱ 1.5 ሚሊዮን ያህል ኢትዮጵያውያን መፈናቀላቸውንና ሁሉም  በአገር ውስጥ የተፈናቀሉ እንደሆኑም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2566 times