Print this page
Saturday, 01 June 2019 00:00

የማንያዘዋል እንደሻው “እምዬ ብረቷ” ቴአትር ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሊጀመር ሲቃረብ እ.ኤ.አ በ1939 ዓ.ም በአልቶርድ ብረሽድ የተፃፈውና በእውቁ የቴአትር አዘጋጅና በብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ማንያዘዋል እንደሻው ተተርጉሞ የተዘጋጀው “እምዬ ብረቷ” የተሰኘ ውርስ ትርጉም ቴአትር ነገ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል፡። የሁለት ሰዓት ርዝመት ያለው ይሄው ትራጄዲ ዘውግ ቴአትር የጦርነትን አስከፊነትና ከጦርነት ምንም ትርፍ እንደማይገኝ የሚያሳይ ጭብጥ ያለው ሲሆን አንዲት እናት በንግድ ስራ ተሰማርታና ለፍታ ያሳደገቻቸውን ልጆቿን በጦነት ስታጣ እንደሚያሳይ የቴአትሩ ተርጓሚና አዘጋጅ ማንያዘዋል እንደሻው ተናግሯል፡፡
ቴአትሩን ለማዘጋጀት ሰባት ወራትን የጀፈ ሲሆን፣ አርቲስት ወለላ አሰፋፋ ፍቅርተ ጌታሁን፣ ተስፋዬ ገ/ሃና፣ መሰረት ህይወት፣ ጌታቸው ስለሺና መስከረም አበራ እንደተወኑበትና ሲሆን ገጣሚና ተዋናይ ዋሲሁን በላይ በረዳት አዘጋጅነት እንደተሳተፉበት ታውቋል፡፡ በምርቃቱ ላይ በርካታ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የጥበብ አፍቃሪያንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉም ተብሏል::



Read 1337 times
Administrator

Latest from Administrator