Saturday, 13 July 2019 11:10

አርሲ ዩኒቨርሲቲ ለአቶ አዳሙ አንለይ የክብር ዶክትሬት ሰጠ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

 ባለፈው ቅዳሜ ተማሪዎቹን ያስመረቀው አርሲ ዩኒቨርሲቲ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ሂውማን ብሪጅ የተባለው አለማቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት በአገሪቱ ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሆስፒታሎችና ክሊኒኮች የህክምና ቁሳቁሶችን በመለገስ ላበረከተው አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት የዋንጫና የምስክር ወረቀት ያበረከተ ሲሆን፣ ለሂውማን ብሪጅ የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ለአቶ አዳሙ አንለይ የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል፡፡
ተቀማጭነቱ በስዊድን የሆነው ሂዩማን ብሪጅ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ፣ በኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና በሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሃመድ ፎርማጆ ተመርቆ ስራ የጀመረውን የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ላለፉት ረጅም አመታት ለበርካታ የህክምናና የትምህርት ተቋማት በመቶ ሚሊዮኖች ብር የሚገመቱ የህክምና መሳሪያዎችንና ቁሳቁሶችን በመለገስ በጤናውና በትምህርቱ ዘርፍ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተነግሯል፡፡

Read 1548 times