Print this page
Monday, 29 July 2019 00:00

የደቡብ ሱዳኑ መሪ፤ እሳቸው በሌሉበት ብሔራዊ መዝሙር እንዳይዘመር ከለከሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር፤ እሳቸው በሌሉበት የአገሪቱ ብሔራዊ መዝሙር እንዳይዘመር የሚከለክል ህግ ማውጣታቸውን የአገሪቱን የማስታወቂያ ሚኒስትር ጠቅሶ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ የሕዝብ መዝሙር ከኤምባሲዎችና ከትምህርት ቤቶች በስተቀር በሌሎች ቦታዎች መዘመር የሚችለው ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በስፍራው ከተገኙ ብቻ እንዲሆን ፕሬዚዳንቱ ባለፈው አርብ ባደረጉት የካቢኔ ስብሰባ ውሳኔ ማስተላለፋቸውን ማስታወቂያ ሚኒስትሩ ማይክል ማኩዌል በይፋ ማስታወቃቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የተለያዩ ባለስልጣናትና ተቋማት የህዝብ መዝሙሩን ዜማና ግጥም በቅጡ ሳይለማመዱ እንደነገሩ ሲዘምሩት እንደሚታዩ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ “ይህም የአገሪቱን ብሄራዊ ክብር የሚነካ ነው፣ ብሄራዊ መዝሙር ፕሬዚዳንቱ በተገኙበት ብቻ የሚዘመር እንጂ ማንም ተራ ዜጋ የሚያበላሸው አይደለም” ብለዋል፡፡
የሳልቫ ኬር መንግስት ፕሬዚዳንቱ በሌሉበት የህዝብ መዝሙር እንዳይዘመር ቢከለክልም፤ ድርጊቱን በፈጸሙ ላይ የሚወሰደውን እርምጃ በተመለከተ ግን ሚኒስትሩ ያሉት ነገር እንደሌለ ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 1464 times
Administrator

Latest from Administrator