Saturday, 27 July 2019 12:37

ኢትዮጵያዊው ቶማስ ሀይሉ ለ‹‹ብላክ ፓንተር›› ፊልም ቪዲዮ ስራ ተመረጠ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በመላው ዓለም አነጋጋሪ ለነበረው ‹‹ብላክ ፓንተር›› ፊልም ማስታወሻ ለሚሆነውና ዋካንዳ አድቨር ታይዚንግ አለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ ለሚሰራው ቪዲዮ ክሊፕ ሥራ ኢትዮጵያዊው ቶማስ ሀይሉ (ቶሚ ፕላሳ) ተመረጠ፡፡ የ27 ዓመቱ ወጣት  የሙዚቃ ሰው ከ40 በላይ  የሙዚቃ ስራዎችን የሰራ ሲሆን ወደ 48 የሚጠጉ የብሄር ብሄረሰቦችን ጭፈራ አሳምሮ እንደሚጫወት ታውቋል፡፡
ቶማስ ሀይሉ (ቶሚ ፕላስ)  ረቡዕ ረፋድ ላይ በካሌብ ሆቴል ከጋምቤላው ወጣት አቀንቃኝ ኤዲኬንዞና ከሰለሞኒክ ኢንተርቴይመንት ጋራ በጋራ በሰጠው መግለጫ፣ ይህን እድል በማግኘቱ የተሰማውን ደስታ ገልጾ በተሰማራበት የሙያ ዘርፍ አገሩን እንደሚያስጠራ በጋዜጣዊ መግለጫው አስታውቋል፡፡ የአፍሮ ቢት ስልተ ምት አቀንቃኙ ወጣት የኢትዮጵያን ሙዚቃ በተለይም ውዝዋዜ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ዳንስና ሙዚቃ ጋር አስማምቶ ለመስራትና አገሩን ለማስተዋወቅ በሚያደርገው ጥረት ይበልጥ ይታወቃል፡፡

Read 1251 times