Print this page
Saturday, 27 July 2019 12:39

የጋዜጠኛ ይርጋ አበበ ‹‹ኢካቦድ›› መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የእውቁ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ይርጋ አበበ አለባቸው ‹‹ኢካቦድ፣ የተዛቡ አገራዊ ትርክቶችና ፍሬያቸው›› መጽሐፍ ከትላንት በስቲያ ሀሙስ ጀምሮ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መጽሐፉ በዋናነት ታላላቅ የፖለቲካ ወጎችን፣ ማህበራዊ ጉዳዮችን፣ የልጅነት ጊዜን፣ እንዲሁም ዋዛና ቁም ነገር የያዙ ነገር ግን አስተማሪ የሆኑ ትርክቶችን የያዘ ዘርፈ ብዙ ስለመሆኑ ተገልጿል፡፡
አሁን በሕይወት በሌለችው ሰንደቅ ጋዜጣ፣ በአሀዱ ሬዲዮና በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች በተለይም በፖለቲካ ትንታኔ ጽሑፎቹና በስፖርት ዝንባሌው የሚታወቀው ጋዜጠኛ ይርጋ አበበ ‹‹የዘመኑ ተመስገን ገብሬ›› የሚያሰኘውን ከእድሜውና ከኖረው በላይ አንብቦና አንሰላስሎ የጻፈውን መጽሐፍ እነሆ በረከት ስለማለቱ አንጋፋው ጋዜጠኛ እና አርታኢ ጥበቡ በለጠ በመጽሀፉ ጀርባ ባስቀመጠው ማስታወሻ አስፍሯል፡፡ በ187 ገፅ የተቀነበበው መጽሐፉ በ67 ብር ከ83 ሳንቲም ለገበያ የቀረበ ሲሆን ጃፋር መጻህፍት መደብር በዋናነት እያከፋፈለው ይገኛል::

Read 1171 times
Administrator

Latest from Administrator